13/07/2026
📣 ለመገናኛ ብዙሃን !
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ከዋና አሰልጣኝ ሹመት እና በክለቡ ወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ሀሙስ - ሀምሌ 9/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ላይ ቦሌ በሚገኘው "ስካይ ላይት ሆቴል" ጋዜጣዊ መግለጫ ስለምንሰጥ በቀኑና በሰዓቱ ተገኝታችሁ የሚድያ ሽፋን እንድትሰጡ በማክበር እንጠይቃለን ።
13/07/2026
💪 ተስፋዎቻችን የደርቢ ድል አስመዝግበዋል!
🟤የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፈደሬሽን ከ17 ዓመት በታች ውድድር የጨዋታ ውጤት
🟡 ኢትዮጵያ ቡና 2️⃣-0️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ
⚽️ብርሃን ታምራት
⚽️ ተሻገር አሸናፊ
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ
👉 https://t.me/coffeefc
12/07/2026
🚨 በዝምታ የሚሠራን ክለብ በጭምጭምታ አናረብሽ!
ከአሰልጣኝ ገብረመድህን ሐይሌ ፊርማ በኋላ፣ ከተደበቁበት የወጡ አንዳንዶች እንደተለመደው "የዝውውር መረጃ" በሚል ስም የትኩረት ማዕከላቸውን እንደገና ወደ ኢትዮጵያ ቡና ላይ ማድረግ ጀምረዋል።
"ጭምጭምታ" የሚባል የጋዜጠኝነት መርህ የለም። አንድ ጋዜጠኛ እርግጠኛ በሆነ መረጃ ላይ ተመስርቶ ዜና ማቅረብ እንጂ፣ ያልተረጋገጠ ወሬን "ጭምጭምታ" በሚል ስም ማሰራጨት ከአሉባልታ አይለይም።
የሚያስገርመው ግን የዝውውር ወሬዎች ሲነሱ በዋነኝነት የሚጠቀሰው ኢትዮጵያ ቡና ብቻ መሆኑ ነው። ሌሎች ክለቦችስ የዝውውር ሂደት የላቸውም? ወይስ ጭምጭምታ ሲወራ የሚደምቀው በኢትዮጵያ ቡና ብቻ ሲሆን ነው?
አንዳንዶች ደግሞ የሚገርመው ከክለቡ ቦርድ ጋር ተቀምጠው የወሰኑ ይመስል፣ የአሰልጣኙን ደመወዝ፣ የተጫዋቾችን ዝውውር፣ የድርድር ሂደት እና መዳረሻ በእርግጠኝነት ሲያወሩ ነው።
እውነታው ግን ግልጽ ነው፤ ብዙዎች የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በማህበራዊ ሚዲያ ያላቸውን ተፅዕኖ ተጠቅመው የራሳቸውን ወሬ ለማስፋፋትና ትኩረት ለማግኘት የሚደረግ የድለላ ስራ ነው ።
👉አሁንም ለደጋፊዎች
ከባለፉት ዓመታት ተምረናል። ክለባችን በዝምታ ሲሠራ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ አይተናል። ስለዚህ ለአንዳንዶች የፌስቡክ ማድመቂያ፣ ለወሬ ማሞቂያ ወይም ለልተረጋገጠ ዜና ማጣፈጫ ከመሆን እንቆጠብ።
ያልተረጋገጠ ወሬና "ጭምጭምታ" በሚል የሚቀርቡ ጽሑፎችን ሳናጣራ ከመለጠፍና ከማጋራት እንቆጠብ።
አሁን የሚያስፈልገን አንድ ነገር ብቻ ነው — ክለባችን በዝምታ እንዲሠራ መፍቀድ። እስካሁን የመጣንበት መንገድ ውጤታማ ነው፤ እሱንም እንቀጥል።
የእኛ ኃይል ድምፃችን ብቻ ሳይሆን ትዕግሥታችንም ነው።
"ዝምታ ብዙ ጊዜ ከጩኸት የበለጠ ውጤት ያመጣል።"
ከቡና_ሠማይ_ሥር
10/07/2026
🇪🇹👉 በቃል ጨርሰናል አንዳንድ የወረቀት ስራዎች ግን ይቀሩናል !!!
አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ
👉 የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊ በትዕግስት ከጎኔ እንዲሆን ጥሪ አደርጋለሁ
👉 ኢትዮጵያ ቡና በአለፉት ሁለት አመታት አምስት አሰልጣኞችን ቢቀያይርም አይደለም አሸናፊ ቡድን ሊፈጥር ሜዳ ላይ ብልጫ መውሰድ አቅቶት ደጋፊውን ከሜዳ እያሸሸው ነበር ::
👉 አሁን አዲሱ የክለቡ ፕሬዚዳንት ክለቡን ለማጠናከር እና የዋንጫ ቡድን ለመስራት በወሰነው መሰረት በይስማ ሸዋ የሚመራው ቦርድ የአገሪቱ ምርጥ አሰልጣኝ ከሆኑት አንዱ ገብረመድን ኃይሌን የክለቡ አሰልጣኝ አድርገው ሾሟል :: ናይል ስፖርት ሚዲያም እውነቱን ለማጣራት ወደ አሰልጣኝ ገብረመድን ሀይሌ በመደወል እንደሚከተለው አነጋግራዋለች
ጥያቄ - ሰላም ነህ አሰልጣኝ ገብሬ እንኳን ወደ ታላቁ ክለብ ኢትዮጵያ ቡና በሰላም መጣህ !!
አሰልጣኝ ገብሬ : ሰላም ነህ አንዳርጋቸው አመሰግናለሁ
ጥያቄ - አሁን አሰልጣኝ ገብሬ የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ነው ማለት ይቻላል ?
አሰልጣኝ ገብሬ :- ( ደስ በሚል ስሜት ውስጥ ሆኖ ) ይቻላል !! በእርግጥ በቃል ነው የጨረስነው አንዳንድ የወረቀት ስራዎች ይቀራሉ
ጥያቄ - ስምህ ከብዙ ክለቦች ጋር ተያይዞ ነበር እንዴት ኢትዮጵያ ቡናን መረጥክ
አሰልጣኝ ገብሬ - እውነቱን ለመናገር አሁን በኢትዮጵያ ቡና አመቺ የስራ መንፈስ አለ በፊት ም የነበሩ አሁንም የመጡ ሁሉ ለስራዬ አጋዥ እንደሚሆኑ ስላመንኩ ነው ታድያ ይህ ከተሟላ በዝህ ደጋፊ መሀል ማን መስራት ይጠላል !!!
ከደጋፊ - ከደጋፊ ምን ትጠብቃለህ?
አሰልጣኝ ገብሬ :- በትዕግስት ከጎኔ እንዲሆኑ ነው ሁላችንም በድርሻችን ተባብረን ኢትዮጵያ ቡናን ለድል ለማብቃት መስራት ይኖርብናል
ጥያቄ - ስለነበረን ቆይታ አመሰግናለሁ በሚቀጥለው አመት መልካም የውድድር ግዜ ይሁንልህ !!!
አሰልጣኝ ገብሬ - እኔም አመሰግናለሁ !!!
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ
👉 https://t.me/coffeefc
09/07/2026
🖤💛 እንኳን ደስ ያላችሁ
የወልዋሎ አዲግራት ዮኒቨርሲቲ እግር ኳስ ቡድን የ2018 ዓም የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል!
ለመላው የክለቡ ተጫዋቾች፤ደጋፊዎች፤የክለቡ አመራሮች እንኳን ደስ አላችሁ!
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ!
07/07/2026
👉ክለብህን ከደላሎች እና አዋቂ ነን ባዮች ጠብቅ!!
ያንን ክፉ ስራቸውንና መርዛቸውን ለመርጨት ስራ ጀምረዋል በርበሬዎቹ በሚል ፔጅ መጥተዋል ውል ያለውን ተጨዋች እዚህ እዛ ሊፈርም ነው ማለት ጀምረዋል ትላንት በነዱበት መንገድ ዛሬም ስም ቀይረው ሊያሽከረክሩ መጥተዋል እምቢኝ በላቸው ዝም በል በላቸው ይሄ የአመራር ስራ ነው ስራውን ለሰሪው ሰጥተን ለጠላቶችህ እኛ አለን እንበለው ክለባችንን ከኛ ሌላ ለኢትዮጵያ ቡና መከታ የለውምና!!
👉ማነህ? ማነሽ? ደላላ ደላሊት ወሬ በመንዛት ጊዜሽን አትግደይ ዋጋ ለማዋደድ አትጣደፊ ይህ ትውልድ ነቅቷል ኢትዮጵያ ቡና የጨረታ መነሻ አይደለም እጃቹን ከክለባችን አንሱ ይህ ፍም የሆነ እሳት ትውልድ እንዳይለበልብህ ተጠንቀቅ።
06/07/2026
🇪🇹👉 ኢትዮጵያ ቡና እና አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ተለያይተዋል !!!
👉 ኢትዮጵያ ቡና በሚቀጥለው አመት ሜዳ ላይ ብልጫ ወስዶ የሚያሸንፍ ቡድን ለመስራት እና ደጋፊውን ወደ ስታዲየም ለመመለስ ቆርጪ እሰራለው ብሏል ::
👉 ለዝህም ፈጠን ያለ ውሳኔ በመወሰን ከአሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ጋር በስምምነት መለያየቱ ታውቋል !!
👉 በሌላ በኩል ክለቡ ምርጥ ብቃት ያለው ሜዳ ላይ ለውጥ የሚያመጣ በስነምግባሩ የተመሰገነ እና ይህን አንጋፋ ክለብ የሚመጥን አሰልጣኝ ደጋፊው ይፈልጋል !!!
06/07/2026
🏆 የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባዘጋጀው የ2018 ዓ.ም የሴቶች ከፍተኛ ዲቪዚዮን ውድድር ያላለቁ ጨዋታዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ ቡና የውድድሩ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል! 🥇
ይህንን ተከትሎ በውድድሩ ሂደት ላቅ ያለ ብቃት ያሳዩና የኮከብነት ክብርን የተጎናጸፉ ተጫዋቾች እና አሰልጣኝ ተሸላሚ ሆነዋል፦
🌟 ኮከብ ተጨዋች:
• ሳኒያ አቡበከር — ኢትዮጵያ ቡና
🧤 ኮከብ ግብ ጠባቂ:
• ብዙዓየሁ ደጀኔ — ኢትዮጵያ ቡና
⚽ ኮከብ ግብ አግቢ:
• አበባ ደመቀ — ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ኮከብ አሰልጣኝ:
• አሰልጣኝ ቶሎሳ ብርብርሳ — ኢትዮጵያ ቡና
ለሻምፒዮኑ ኢትዮጵያ ቡና እና ለኮከብ ተሸላሚዎች በሙሉ ለአገኙት ታላቅ ስኬት የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ልባዊ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላልፋል!
Via
03/07/2026
⌛ የመጀመሪያ አጋማሽ
⚽ ወላይታ ድቻ 0️⃣-0️⃣ ኢትዮጵያ ቡና
👆🏾👆👆🏾👆
👆🏾👆