Halaba Tube

Halaba Tube

Share

Develope on

06/07/2026

የዛላ ካፕ የነገ ማክሰኞ ጨዋታዎች
አምር ዳቦ 🆚 ሀላባ ፍራፍሬ
4:00 ሰዓት
እድገት 🆚 ኒሃ
9:30 ሰዓት
ዘቡራ ዱቂት ፋብሪካ 🆚 አቡ ሀማስ ስፔር
11:00 ሰዓት

06/07/2026

የቀይ ዛላ ካፕ 2018 ውድድር የሀላባ ዞን ሚዲያ የቁሊቶ አሽከርካሪዎችን 2 ለ0 እየመራ ቢቆይም በጥቃቅን ስህተቶች በተቆጠረበት ሁለት ግብቦች በአቻ ተጠናቋል

በጨዋታው ድንቅ ብቃቱን ያሳየው ግብ ጠባቂው ሪባቶ የጨዋታው ኮከብ መሆን ችሏል።

ሀላባ ዞን ሚዲያ 2 - 2 ቁሊቶ አሽከርካሪ

05/07/2026

የቀይ ዛላ ካፕ 2018 የምድብ 2ኛ ጨዋታ ትንቅንቁ የነገው ታላቅ ፍልሚያ የመጀመሪያው ጨዋታ ትዝታው ገና ሳይለቅ የደጋፊው ደማቅ ድባብ እነሆ የዛላ ካፕ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ነገ ሰኞ ቀጥሎ ይውላል...!
ሰኞ
ጠዋት 4 ሰዓት
ሀላባ ዞን ሚዲያ 🆚 ቁሊቶ አሽከርካሪ

ከሰዓት 9:30
አረፋት ፋርማሲ 🆚 ግሪኖች

11:00 ሰዓት
ዲኤች 🆚 ኖክ ገደባ

ነገ የሚደረገው ጨዋታ ከመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ሰከንድ ድረስ ከፍተኛ ፉክክር የሚታይበት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። እያንዳንዱ ኳስ እያንዳንዱ ሙከራ እና እያንዳንዱ መከላከል የዋንጫውን ባለቤት ለመወሰን ትልቅ ሚና አላቸው። የስሜት ማዕበል የኳስ ጥበብ ነገ በሜዳ ላይ ይገለጣል የምትደግፉት ቡድን ለዚህ ታላቅ ፍልሚያ ምን ያህል የተዘጋጀ ይመስልዎታል?
የነገውን ታላቅ ጨዋታ ለመታደም በሰዓቱ ይገኙ ድባቡን በአካል ተገኝተው ይመስክሩ!

Photos from Halaba Tube's post 05/07/2026

የቀይ ዛላ የካፕ 2018 ውድድር በታላቅ ድምቀት ዛሬ ተጀመረ
የቀይ ዛላ ስፖርት ክለብ 34 አመት የምስረታ ፌስቲቫል
ሀላባ ቀሊቶ ሰኔ 28 /2018 እሁድ
መላው የስፖርት አፍቃሪ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው ታላቁ የቀይ ዛላ ካፕ ውድድር በዛሬው እለት በደማቅ ስነ ስርዓት ጅማሮውን አድርጓል። ዛላ ሜዳ በደማቅ ቀለማት አሸብርቆ የዋለ ሲሆን ደጋፊዎች ያሳዩት ልዩ ድምቀት እና ስሜት ውድድሩን ይበልጥ ማራኪ አድርጎታል። ገና ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ የታየው ብርቱ ፉክክር እና የተጫዋቾች ፍልሚያ የዘንድሮው የዛላ ካፕ ውድድር እጅግ አስገራሚና ያልተገመቱ ውጤቶች የሚመዘገቡበት ለመሆኑ ማሳያ ሆኗል። የውድድሩ መክፈቻ በደጋፊዎች ዘንድ በነበረው ከፍተኛ መነሳሳት በአስደናቂ ድባብ ልዩ ድምቀት አግኝቷል። ስነ ስርዓቱን ለመታደም ቀደም ብለው ዛላ ሜዳ የተገኙት ደጋፊዎች በነበራቸው ድጋፍ የዕለቱን መርሃ ግብር ወደ ላቀ ስሜት አሸጋግረውታል። በክብር እንግዶቹ አቀባበል እና በደጋፊዎቹ ማራኪ ድጋፍ የተጀመረው ይህ ውድድር በቀጣዮቹ ቀናት ብርቱና አዝናኝ ፉክክሮች እንደሚስተናገዱበት ትልቅ ማሳያ ሆኖ አልፏል።

ዋንጫውን ማን ያነሳል? የሚለው ትንቅንቅ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል

05/07/2026

የዛላ ካፕ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ
ተጠናቋል

03/07/2026

ኑዝላ የመድሀኒት እና የህክምና መሳሪያዎች ጅምላ አከፋፋይ!🔬🩺

📍አድራሻ:- አዲሱ ለማት ማህበር ፊትለፊት አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ G+1 ላይ ይገኛሉ

📲ስልክ:- 0925682983

Photos from Halaba Tube's post 03/07/2026

አስደሳች ዜና ለስፖርት አፍቃሪያን በሙሉ አጓጊውና ተናፋቂው የክረምት ውድድር የሚጀምርበት ምዝገባ ጊዜ ይፋ ሆነ
=====

ሰኔ 26/2018 #በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የ2018 ዓ/ም የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት እና የስፖርት አሶሴሽኖች በጋራ በመሆን የሚያዘጋጁት የክረምት ወራት ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ምዝገባ የሚጀምርበት ጊዜ #ከስኔ 29/2018 ዓ/ም እስከ #ሀምሌ 06/11/18 ዓ/ም መሆኑ ይፋ ሆነዋል።

የእግርኳስ ክለቦች ለምዝገባ ሲመጡ ማሟላት ያአለባቸው መስፈርት እንደሚከተለው ቀርቧል።

1. ከሀላባ ቁሊቶ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በተሰጠው የተጫዋቾች የውል ፎርም መሰረት የክለብ ተወካይ፣ የጽ/ቤቱ ተወካይ የፈርሙበት ፎርምና ጽ/ቤቱ ማዕተብ ያአለበት ፎርም ከምዝገባው ቀደም ብላችሁ ለውድድር አዘጋጅ ማቅረብ አለባቸው።

2. ከ13 ዓመት በታች ተወዳዳሪ ክለቦች የክለብ አባላት 18 ተጫዋች፣ 1 ወጌሻ፣ 1 ቡድን መሪ እና 2 አሰልጣኞች በድምሩ 22 የክለብ አባላት ማስመዝገብ አለባቸው።

3. በሌሎች የእድሜ ክልል ተሳታፊ ክለቦች የክለብ አባላት 22 ተጫዋች፣ 1 ወጌሻ ፣ 1 ቡድን መሪና 2 አሰልጣኞች በድምሩ 26 የክለብ አባላት በኮምፒዩተር የተጻፈ የቡድን አባላት ሰም ዝርዝር ማቅረብና ማስመዝገብ አለባቸው /

4. በእጅ የተጻፈ የቡድን አባላት ስም ዝርዝር ተቀባይነት የለውም።

5. በየዕድሜ ክልል የሚገኙ ክለቦች የመመዝገቢያ ገንዘብ የሀላባ ቁሊቶ ስፖርት ም/ቤት በሀላባ ቁሊቶ ንግድ ባንክ በተከፈተው አካውንት ላይ በማስገባት ደረሰኝ በመያዝ ለመመዝገብ መቅረብ አለባቸው።

6. የክለብ ስም ስያሜ ከኢትዮጵያ ስፖርት ፖሊሲ ጋር የሚጻረሩ የክለብ የስም ስያሜ ይዞ መቅረብ አይቻልም

7. ክለቦች ለምዝገባ ሲመጡ ከሚገኙበት ቀበሌ እና ቀጠና የድጋፍ ደብዳቤ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።

8. አንድ ክለብ 5 ሀላፊነቱ የሚወስዱ ግለሰቦችን ማቅረብ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል። በተጨማሪም በክለባቸው ውስጥ የሰለጠነ አስልጣኝ እና ባለሙያዎች ሊኖራቸው ይገባል።

9. የምዝገባ ጊዜ አስገዳጅ ሁኔታ ካልተፈጠረ በቀር በማስታወቂያ ከተገለፀው ቀን በኋላ የሚመጣ ክለብ ተቀባይነት የለውም።

" ተተኪ ታዳጊ ወጣቶች እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሚሆኑ ስፖርተኞች ለማፍራት በቅንጅት እንሰራለን ።"

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት

26/06/2026

መቐለ 70 እንደርታ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዷል !

በ2010 የውድድር ዓመት ወደ ፕሪምየር ሊጉ አድጎ ላለፉት ዓመታት በዋናው ሊግ ሲሳተፍ የቆየው የ2011 ቻምፕዮኑ መቐለ 70 እንደርታ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ቡና የ ሦስት ለባዶ ሽንፈት ማስተናገዱ ተከትሎ ከፕሪምየር ሊግ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዷል።

26/06/2026

3ተኛ ወራጅ ድሬዳዋ ሆኗል ከ11 አመታት በኃላ CBE ተሰናብቷል

Photos from Halaba Tube's post 26/06/2026

በሀላባ ከተማ የሚገኙ የአርሰናል ደጋፊዎች የሀላባ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ለማጠናከር 50 ሺህ ብር ገቢ አደረጉ

የሀላባ ከነማ ሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ተከትሎ የገቢ መሰብሰቢያ ቻሌንጅ ተጀምሮ ገቢ እየተሰበሰበ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን ሁሉም ከዚህ ቀደም በግል የገቢ አሰባሰቡን ከተቀላቀሉት በተጨማሪ በሀላባ ከተማ የሚገኙ የአርሰናል ደጋፊዎች ስም በአንድነት 50,000 ብር ገቢ አድርገዋል።

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Alaba K'ulito?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Southern
Alaba K'ulito