15/06/2026
ግብጽ እና ቤልጂዬም አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ምድብ ጨዋታ ግብጽ እና ቤልጂዬም 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from FMC Sport, Sports, Addis Ababa.
15/06/2026
ግብጽ እና ቤልጂዬም አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ምድብ ጨዋታ ግብጽ እና ቤልጂዬም 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
15/06/2026
ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ስምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ለዓለም ዋንጫ አሸናፊነት ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የሆነችው ስፔን ከኬፕ ቨርዴ ጋር ባደረገችው የውድድሩ የመጀመሪያ ጨዋታ አቻ ተለያይታለች።
በጨዋታው የስፔን ተጫዋቾች ግብ ለማስቆጠር በተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም የኬፕ ቨርዴን መረብ መድፈር ሳይችሉ ቀርተዋል።
15/06/2026
አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርባምንጭ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አቡዱልራህማን መሐመድና ቴዎድሮስ አጨ አስቆጥረዋል፡፡
በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ሀዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግቦች አለኝታ ማርቆስ እና ሮሆቦት ስላሎ አስቆጥረዋል፡፡
ሀዋሳ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ደግሞ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል።
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡
15/06/2026
ሪያል ማድሪድ ኩኩሬላን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ስፔናዊው የግራ መስመር ተጫዋች በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡
ሪያል ማድሪድ ለ27 ዓመቱ ተጫዋች 55 ሚሊየን ዩሮ እና እየታየ የሚጨመር 5 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ የሚከፍል ይሆናል፡፡
ኩኩሬላ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ2022 ከብራይተን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
ተጫዋቹ በቼልሲ በነበረው ቆይታ የኮንፈረንሰ ሊግ እና የዓለም ክለቦች ዋንጫዎችን ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡
15/06/2026
በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፈው ኬፕ ቨርዴ ከስፔን…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡
በምድብ 8 የመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን የምታደርገው አፍሪካዊቷ ኬፕ ቨርዴ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ከስፔን ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በኦፕታ ቅድመ ትንተና መሰረት የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ እንደምታነሳ ቅድመ ግምት አግኝታለች፡፡
በዚሁ ምድብ የሚገኙት ሳዑዲ አረቢያ እና ዩራጋይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በምድብ 7 የተደለደሉት ቤልጂየም ከግብፅ ምሽት 4 ሰዓት እንዲሁም ኢራን ከኒውዚላንድ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
15/06/2026
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ነገሌ አርሲ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ነገሌ አርሲ በዛሬው ጨዋታ ነጥብ የሚጥል ከሆነ ሲዳማ ቡና ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
15/06/2026
ታሪክ ሰሪዋ ኩራሳኦ
ከደቂቃዎች በኋላ በኤክስትራ ታይም ስፖርት ቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን
#ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን فانا_عربي_بودكاست
15/06/2026
ኮትዲቫር ኢኳዶርን 1 ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ኮትዲቯር ኢኳዶርን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።
የኮትዲቯርን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ የማንቼስተር ዩናይትዱ አማድ ዲያሎ አስቆጥሯል።
14/06/2026
ኔዘርላንድስ እና ጃፓን አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ኔዘርላንድስ እና ጃፓን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
14/06/2026
ጀርመን ኩራሳኦን 7 ለ 1 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ጀርመን ኩራሳኦን 7 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች፡፡
በጨዋታው ካይ ሀቨርትዝ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል።
ቀሪዎቹን የጀርመን ግቦች ደግሞ ንሜቻ ፣ ኡንዳቭ፣ ሙሴይላ፣ ሽሎተርቤክና ብራውን ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ኮሜንስያ ደግሞ ለትንሿ የካሪቢያን ደሴት ኩራሳኦ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ የሆነችውን ግብ አስቆጥሯል፡፡