FMC Sport

FMC Sport

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from FMC Sport, Sports, Addis Ababa.

Photos from FMC Sport's post 15/06/2026

ግብጽ እና ቤልጂዬም አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ምድብ ጨዋታ ግብጽ እና ቤልጂዬም 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

Photos from FMC Sport's post 15/06/2026

ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ስምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

ለዓለም ዋንጫ አሸናፊነት ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የሆነችው ስፔን ከኬፕ ቨርዴ ጋር ባደረገችው የውድድሩ የመጀመሪያ ጨዋታ አቻ ተለያይታለች።

በጨዋታው የስፔን ተጫዋቾች ግብ ለማስቆጠር በተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም የኬፕ ቨርዴን መረብ መድፈር ሳይችሉ ቀርተዋል።

Photos from FMC Sport's post 15/06/2026

አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርባምንጭ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አቡዱልራህማን መሐመድና ቴዎድሮስ አጨ አስቆጥረዋል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ሀዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግቦች አለኝታ ማርቆስ እና ሮሆቦት ስላሎ አስቆጥረዋል፡፡

ሀዋሳ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ደግሞ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል።

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

15/06/2026

ሪያል ማድሪድ ኩኩሬላን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ስፔናዊው የግራ መስመር ተጫዋች በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡

ሪያል ማድሪድ ለ27 ዓመቱ ተጫዋች 55 ሚሊየን ዩሮ እና እየታየ የሚጨመር 5 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ የሚከፍል ይሆናል፡፡

ኩኩሬላ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ2022 ከብራይተን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በቼልሲ በነበረው ቆይታ የኮንፈረንሰ ሊግ እና የዓለም ክለቦች ዋንጫዎችን ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡

Photos from FMC Sport's post 15/06/2026

በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፈው ኬፕ ቨርዴ ከስፔን…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በምድብ 8 የመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን የምታደርገው አፍሪካዊቷ ኬፕ ቨርዴ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ከስፔን ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በኦፕታ ቅድመ ትንተና መሰረት የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ እንደምታነሳ ቅድመ ግምት አግኝታለች፡፡

በዚሁ ምድብ የሚገኙት ሳዑዲ አረቢያ እና ዩራጋይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በምድብ 7 የተደለደሉት ቤልጂየም ከግብፅ ምሽት 4 ሰዓት እንዲሁም ኢራን ከኒውዚላንድ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

15/06/2026

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ነገሌ አርሲ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ነገሌ አርሲ በዛሬው ጨዋታ ነጥብ የሚጥል ከሆነ ሲዳማ ቡና ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

15/06/2026

ታሪክ ሰሪዋ ኩራሳኦ

ከደቂቃዎች በኋላ በኤክስትራ ታይም ስፖርት ቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን


#ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን فانا_عربي_بودكاست

Photos from FMC Sport's post 15/06/2026

ኮትዲቫር ኢኳዶርን 1 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ኮትዲቯር ኢኳዶርን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።

የኮትዲቯርን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ የማንቼስተር ዩናይትዱ አማድ ዲያሎ አስቆጥሯል።

Photos from FMC Sport's post 14/06/2026

ኔዘርላንድስ እና ጃፓን አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ኔዘርላንድስ እና ጃፓን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

Photos from FMC Sport's post 14/06/2026

ጀርመን ኩራሳኦን 7 ለ 1 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ጀርመን ኩራሳኦን 7 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፋለች፡፡

በጨዋታው ካይ ሀቨርትዝ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል።

ቀሪዎቹን የጀርመን ግቦች ደግሞ ንሜቻ ፣ ኡንዳቭ፣ ሙሴይላ፣ ሽሎተርቤክና ብራውን ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ኮሜንስያ ደግሞ ለትንሿ የካሪቢያን ደሴት ኩራሳኦ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ የሆነችውን ግብ አስቆጥሯል፡፡

Want your business to be the top-listed Gym/sports Facility in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address

Addis Ababa