12/07/2026
ዛሬ 3ኛ ዙር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ማጠቃለያ ጉባኤ ማካሄድ ጀምረናል።
ምክር ቤቱ ያጸደቃቸው አጀንዳዎች:-
1. የምክር ቤቱን 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
2. የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
3. የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
4. የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት 2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም እና የኦዲት ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
5. የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
6. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2019 በጀት አዋጅ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
7. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና ካሳ ጉዳዮች ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ እንደገና ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፤
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
12/07/2026
የተቋም ግንባታ እና አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ
የከተማ አስተዳደሩ የተቋማት አገልግሎት እንዲዘምን በሰጠው ልዩ ትኩረት መሰረት ዋና መስሪያ ቤትን ጨምሮ 11 አዲስ "መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ተከፍተዉ ወደ ስራ በመግባታቸዉ 150 የሚሆኑ አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡
ከዚህ ጎን ለጎን ከ8 ተቋማት የተለዩ 41 የሚደርሱ አገልግሎቶች በከተማው ውስጥ ህዝብ በሚበዛባቸው አደባባዮች በመገኝት ተንቀሳቃሽ የአዲስ መሶብ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በአዲስ መሶብ ማዕከላት እስካሁን 262,784 በላይ ለሚሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ በእነዚህ ማእከላት የተገለገሉ የተገልጋዮች እርካታ በአማካይ 99 በመቶ ደርሷል።
ወደ ማእከሉ ያልገቡ 45 አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ በማድረግ አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ አጠቃላይ በዲጂታል የሚሰጡ አገልግሎቶችን ወደ 392 ማሳደግ ተችሏል፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
07/07/2026
የትግራይን አሁናዊ ሁኔታ በሚመለከት፦
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በርካታ ጥቅሞችን ያስገኘ ቢሆንም፣ ለምን ተስማማችሁ በሚል ያኮረፉ በርካታ ኃይሎች ተፈጥረዋል። ከሕወሓት ባሻገር፤ በትግራይ ላይ ጥፋት ሊቀጥል ይገባ ነበር ብለው የሚያስቡ አካላት በማኩረፍ ከእኛ የራቁ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ እርስ በእርስ ለመተባበር የሞከሩበት ሁኔታ አለ።
አሁን ላይ በትግራይ ባሉ ኃይሎች በየቀኑ አዳዲስ ግጭቶችንና ጦርነትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ ትንኮሳዎች እየተፈጸሙ ይገኛሉ። ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነውና የከፋው ጉዳይ ግን በአሁኑ ወቅት በርካታ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍሰው በሱዳን እየተካሄደ ላለው ጦርነት እንዲሰለፉ መደረጉ ነው። እነዚህ ወጣቶች በማያውቁትና በማይመለከታቸው ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ሕይወታቸውን እያጡ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ሳይበቃ፣ ጉዳዩ ወደ ሱዳንም ተሻግሯል።
በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ የችግሩ ፈጣሪ ሳይሆን፣ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ነው። የትግራይን ሕዝብ ይበልጥ የጎዳውና ጉዳቱን ያባባሰው የማይታይ የውስጥ ቁስል መኖሩ ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ የውስጥ ቁስል ደግሞ በቀላሉ የማይሽር ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዛሬ በትግራይ ውስጥ ከሚኖረው ይልቅ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ እና በአዳማ በሰላም እየኖረና ያለምንም ስጋት ወጥቶ የሚገባው የትግራይ ተወላጅ ቁጥር ይበልጣል።
#የጠሚሩምላሾች
07/07/2026
የሰላም ጥሪ ለትግራይ
በመጀመሪያ ደረጃ የሚያስፈልገን ሰላም፣ ትብብር እና አብሮ መስራት ነው። በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው አካላት ቢኖሩም፤ ጦርነት አውዳሚና ትርፍ የለሽ በመሆኑ እምቢ ብለናል። አሁንም ቢሆን ለሰላም፣ ለንግግርና ለውይይት በራችን ምንጊዜም ክፍት ነው። የራሳችንን ጥቅም መስዋዕት አድርገንና ተጎድተን እንኳ በትግራይ ዘላቂ ሰላም የሚመጣ ከሆነ ዋነኛ ፍላጎታችን እርሱ ብቻ ነው። እርስ በርስ መጠላለፍና መውደቅ ማንንም አይጠቅምም።
ይሁን እንጂ ለትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚመጣው የሕወሓት አመራሮች በወጣቶቻቸው ላይ እምነት ጥለው ለተተኪው ትውልድ ዕድል መስጠት ሲችሉ ብቻ ነው። የመደመር መንግሥት ዋነኛ መሻትና ግብ በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች ላይ የሚታየው ልማትና ዕድገት በትግራይም ተደራሽ ሆኖ ማየት ነው።
#የጠሚሩምላሾች